የዚህን እትም የሮዝ፣ ይቅርታ የ“አዲስ ጉዳይ”፣ ጽሑፌን በሌላ ርዕስ ላይ እያዘጋጀኹ ነበር። በመካከሉ የአሜሪካ ድምጽ ለመስማት ከፍቼ መስማት ጀምሬ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የአንድ ወዳጄ ስልክ አንቃጨለ። ሳነሳው የአሜሪካ ድምጽን ለመስማት ሞክሮ እንዳልተከፈተለት ነገረኝ። “ኧረ እየሰማኹ ነው፤ እስቲ ድጋሚ ሞክረው” አልኩት። ሞከረው። አይሰራም። እኔም እሰማው የነበረውን ትቼ ድጋሚ ሌላ ስከፍት እውነትም ሌላ ሆኗል። ድረ ገፁ ግን ራሱ የአሜሪካ ድምጽ ነው። የሚታየው ግን የተለመደው የቪ.ኦ.ኤ ዓርማ ሳይሆን በአረብኛ ያሸበረቀ “እኛም እንደምንችል አሳየናችሁ” የሚል ፉከራ ቢጤ ነው።
Monday, February 28, 2011
Saturday, February 26, 2011
ጥያቄና መልስ
“ከወዴት አገር ነህ ከየትኛው ሥፍራ፣
ከየትኛው መንደር ከየትኛው ጋራ፣
እስቲ ስላገርህ፣
ንገረን እባክህ?”
የትኛውን ልጥቀስ የትኛውን ብዬ፣
የትኛውን ላንሣ የትኛውን ጥዬ፣
የትኛው ይሻላል ከየቱ ልነሣ፣
የቱን ላስታውሳቸው የትኛው ይረሣ?
Friday, February 25, 2011
አሜሪካዊ ከሆንክ መንግሥትህ ይደርስልሃል፣ ኢትዮጵያዊ ከሆንክ...
ሊቢያ ሰሞኑን እንዲህ መዓት ሲነድባት የሌሎች አገራት መንግሥታት ደግሞ በዚያ የሚኖሩ ዜጎቻቸውን ለመታደግ መርከቦቻቸውን እና ጀልባዎቻቸውን አሰልፈዋል። ቱርክ እና ቻይና መርከቦቻቸውን ሲሞሉ ተመልክቻለኹ። አሜሪካ ገና ዜጎቿን ጠቅልላ አላወጣችም። ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ትናንት ተናገሩ እንደተባለው ከምንም ነገር በፊት ቅድሚያ የሚሰጡት “የዜጎቻቸው ደኅንነት” ነው። እንግዲህ የሊቢያውን የሰሞኑን ሁኔታ በመሰለ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ስትወድቅ አሜሪካዊ ከሆንክ መንግሥትህ ያወጣሃል፣ ኢትዮጵያዊ ከሆንክ ደግሞ ፈጣሪ ብቻ ይደርስልሃል።
Wednesday, February 23, 2011
ዘመናዊ የሴቶች ባርነት በዱባይ - የኢትዮጵያውያቱ ሕይወት
ይህ የኢትዮጵያውያት እህቶቻችንን የዱባይ (የአረብ አገሮች) ሕይወት የሚያሳይ ዝግጅት ነው። ፕሮግራሙን ያቀረበው የጀርመን ቴሌቪዥን ሲሆን፣ አንዱ የበረታ ወገናችን በእንግሊዝኛ ወይም በአማርኛ ተርጉሞ እስኪያሳየን ድረስ ለጊዜው ጀርመንኛ የሚሞክሩ ብቻ የሚያዩት ነው።
Nightmare in Wonderland, Albtraum im Märchenland - Moderne Arbeitssklavinnen in Dubai
Albtraum im Märchenland - Moderne Arbeitssklavinnen in Dubai
Nightmare in Wonderland, Albtraum im Märchenland - Moderne Arbeitssklavinnen in Dubai
Albtraum im Märchenland - Moderne Arbeitssklavinnen in Dubai
Monday, February 21, 2011
Did I witness VOA being Hacked?
A while ago (7pm Eastern Time), I tried to open Voice of America website (http://www.voanews.com/) and amazingly come up with the picture I attached below. It looks like the website was hacked. It also says that following websites are also hacked by Iranians.
Monday, February 14, 2011
“የምክር ቃል”፦ የውጪ አገር ነገር
ባለፈው “በኢትዮጵያ አእምሮ” ያለውን “የአሜሪካ ኑሮ” በተመለከተ አንዳንድ ሐሳቦች ለማካፈል ከሞከርኩ በኋላ ብዙ አበረታች ሐሳቦች እና መልእክቶች ደርሰውኛል። የበለጠ እንድንወያይበት የሚያደርጉ መነሻዎችም አግኝቻለኹ። በተለይም የኒውዮርኩ ወዳጄ ዶ/ር ታዬ ሁሴን ያደረሰኝ “የምክር ቃል” የምትል የቆየች “ምጥን መጽሐፍ” (ትንሽ መጽሐፍ) ርዕሰ ጉዳዩን እንድመለስበት አድርጋኛለች። ይህ መጣጥፍ በዚህቹ መቶ ዓመት ሊሞላት 14 ዓመት በሞላት መጽሐፍ ውስጥ የተካተቱትን ነጥቦች ለማስታወስ ይሞክራል።
Friday, February 11, 2011
አዬ አሜሪካ!
(ተስፋዬ)
በቅርቡ ነው የመጣሁት፡፡ እንደ መታደል ሆኖ አበባ ይዞ የሚቀበል ቤተሰብ ስለተቀበለኝ ዱላስ አውሮፕላን ማረፊያ ኧረ ውሃ በላኝ ብዬ አልጮሁኩም፡፡ ተመስገን ልበላ፤ ለካ ይህም አለ፡፡ እርግጥ በአሜሪካ ፍቅር ጥንብዝ ብዬ የሠከርኩ አልነበርኩም፡፡ ሰው ሆኖ ሆድ የማይብሰው የለምና አንዳንድ ቀን ሆድ ሲብሰኝ የነበርኩበትን ከተማ ብቻ ሳይሆን የምር የማልጨክንባትን እንደ ስዕለት ልጅ የምሳሳላትን ኢትዮጵያን ሳይቀር ጥዬ መውጣት እመኛለሁ፡፡
በቅርቡ ነው የመጣሁት፡፡ እንደ መታደል ሆኖ አበባ ይዞ የሚቀበል ቤተሰብ ስለተቀበለኝ ዱላስ አውሮፕላን ማረፊያ ኧረ ውሃ በላኝ ብዬ አልጮሁኩም፡፡ ተመስገን ልበላ፤ ለካ ይህም አለ፡፡ እርግጥ በአሜሪካ ፍቅር ጥንብዝ ብዬ የሠከርኩ አልነበርኩም፡፡ ሰው ሆኖ ሆድ የማይብሰው የለምና አንዳንድ ቀን ሆድ ሲብሰኝ የነበርኩበትን ከተማ ብቻ ሳይሆን የምር የማልጨክንባትን እንደ ስዕለት ልጅ የምሳሳላትን ኢትዮጵያን ሳይቀር ጥዬ መውጣት እመኛለሁ፡፡
Thursday, February 10, 2011
Wednesday, February 2, 2011
የአንባብያን አስተያየት
ወንድማችን ዲያቆን ኤፍሬም በቅድሚያ የከበረ ሠላምታዬ ይድረስህ። የተነሳው ርዕስ አዲስ ለመጡትም ሆነ ገና ወደ አሜሪካ ለመምጣት ላሰቡ ወገኖቻችን በጣም ጠቃሚ እንደሚሆን አምናለሁ። ምንም እንኳ ብዙዎች ወገኖቻችን የውጭ ሀገር ኑሮ እንዴት አስቸጋሪ እንደሆነ ቢገለጽላቸውም፣ ያለ መታደል ሆኖ እውነታውን ላለመቀበል "እሱ ሀብታም እየሆነ እያየሁት እሱን እንዳልጋፋው፣ እሱን እንዳላስቸግረው፣ ሊረዳኝ ስላልፈለገ ብቻ ክፉ ክፉውን ያወራልኛል" በማለት ራሳቸውን ስለሚደልሉ ወይም ስለሚያሞኙ ከግንዛቤ እጥረት የተነሳ ለአደጋ ሲጋለጡ ይስተዋላል። አንተም ወንድሜ በተለያዩ ምሣሌዎች ችግሮቹን ለማሳየት የበኩልህን ጥረት አድርገሃል።
Tuesday, February 1, 2011
Subscribe to:
Posts (Atom)


