እንዲህ እንደ አሁኑ ዓመታት አልፈው፣ አገር ቤቱም እንደ ጨረቃ
ርቆ፣ ትዝታም የሕልም ያህል ቀጥኖ፣ ልቡና ዛሬን ሳይሆን ትናንትን፣ የዛሬን አዋቂነት ሳይሆን የትናንትን ልጅነት ሲናፍቅ … መስከረም
ሁለትም ከአዲስ ዘመን ተርታ በትዝታ መስኮት መምጣቱ አይቀርም። የኔ ትውልድ፣ የልጅነታችን ወራት ያለፈው፣ ከመስከረም አንድ ይልቅ
መስከረም ሁለት “ርዕሰ ዐውደ ዓመት” ሆኖ ነው። እንቁጣጣሽ ከዘመን መለወጫነቱ ይልቅ የመስከረም ሁለት ዋዜማ መሆኑ የታወቀ እስኪመስል
ድረስ በልጅነት አዕምሯችን የተሳለው ዐቢዩ በዓል የቅ/ዮሐንስ ማግስት ነበር ማለት ይቻላል።
Monday, September 12, 2011
Friday, September 9, 2011
Subscribe to:
Posts (Atom)
.bmp)