(ኤፍሬም እሸቴ - ኢትዮጵያዊ/ READ IN PDF) በኢትዮጵያውያን ዘንድ በታላቅ ሁኔታ ከሚከበሩት በዓላት መካከል ትንሣኤ ወይም ፋሲካ አንዱና ዋነኛው ነው። ሃይማኖታዊ ትርጓሜው እና ምንነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ባህላዊ አከባበሩ እና ምንነቱም ከኢትዮጵያውያን ባህላዊ ማንነት ጋር በጥልቅ የተያያዘ ነው። እንኳን በአገር ቤት ያለው በሰው አገር ያለነውም እንኳን ብንሆን እንደ አቅሚቲ የአገር ቤቱን መንፈስ በያዘ ሁኔታ እናከብራለን። ስለዚህ ፋሲካው መንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን ሥጋዊ/ ባህላዊ አንድምታው ከፍ ያለ ነው ማለት ነው።
አለቃ ዘነብ የተባለው የአጼ ቴዎድሮስ ታሪክ ፀሐፊ አንባቢውን እያዋዛ የመከረበትን “መጽሐፈ ጨዋታ” የተሰኘውን መጽሐፉን “ሥጋዊ ወመንፈሳዊ” (ሥጋዊ እና መንፈሳዊ) እንዳለው ስለ ፋሲካ ያለችኝን ወግ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ ብዬ ብከፍላት ኋላ ለሚከተለው ሐሳብ ጥሩ ገላጭ ይሆናል። ዘነብ ኢትዮጵያዊ ሲል ራሱን እንደገለጸ ኩረጃዬን ሙሉ ለማድረግ ኤፍሬም ኢትዮጵያዊ ብያለሁ፣ ቢያንስ ለዚህ ጽሑፍ። ኢትዮጵያዊነታችንን ከፍ አድርገን በክብር ልናሳይ የሚገባበት ዘመንም ስለሆነ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ይሆንልኛል።
በጥንተ ታሪኩ ፋሲካ የሚጀምረው ከእስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ነጻ የመውጣት ታሪክ ታሪክ ጋር ተያይዞ ነው። ሕዝበ እስራኤል ለረዥም ዘመን በግብጽ አገር በባርነት ሲኖሩ ከቆዩ በኋላ በቤተ መንግሥቱ ያደገው ሙሴ መሪ ሆኗቸው ወደ አገራቸው ለመመለስ የጀመሩትን ጉዞ መሠረት ያደረገ በዓል ነው። ግብጻዊው ገዢ የሚያየውን ተአምራት ተቀብሎ ሕዝቡን ሊለቅ እና ነጻነታቸውን ሊመልስላቸው ባለመፍቀዱ ከተከሰተው ከባዱ ቅጣት ማለትም የግብጻውያኑ የበኩር ልጆች መቅሰፍታዊ ሞት ጋር ይገናኛል።
ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ሞተ በኩር በመጣ ጊዜ ቀሳፊው መልአክ እስራኤላውያን ልጆችን እንዳይቀስፍ እነዚህ ተገዢዎች በየበሮቻቸው መቃን ላይ የበግ ደም ቀብተው፣ ያ መልአከ ሞትም ደሙ የተቀባበትን በር በማለፉና ግብጻውያንን በመምታቱ በዓሉም ከማለፍ ጋር ተገናኘ እና ማለፍን፣ መሻገርንና መሸጋገርን የተመለከተ ሊሆን ቻለ። በዕብራይስጡ “ፓሳህ” ማለት ማለፍ ማለት ነውና። ሁለተኛው ማለትም የክርስቲያኖች ፋሲካ ወይንም ትንሣኤ ደግሞ ክርስቶስ እውነተኛው በግና መስዋዕት ሆኖ ሰዎችን ከጥፋት ወደ ድኅነት ያሻገረበትን ይመለከታል። ለምን ፋሲካ “ሥጋዊ ወመንፈሳዊ” እንዳልኩት ለመረዳት የቀድሞውን የእስራኤል ፋሲካ ከኋላው ከክርስቲያኖች ፋሲካ ጋር ማነጻጸር ነው።
በቀድሞው በእስራኤል ፋሲካም ሆነ በኋለኛው የክርስቲያኖች ፋሲካ፣ “ፋሲካ” አማናዊ ትርጉሙ ከባርነት ነጻ ከመውጣት (ከነጻነት) ጋር የተገናኘ ነው። ይህ ከሆነ ታዲያ ነጻነት ያላት ሥፍራ ምን ያህል ክቡር መሆኑን ያስረዳናል። እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት፣ ከምድራዊ ገዢዎች አስከፊ ተገዢነት ነጻ እንደወጡት ሁሉ በክርስትናው ደግሞ ክርስቶስ የፋሲካው አማናዊ በግ ሆኖ በመሰዋቱ የሰው ልጆች ከሰይጣን ባርነት ነጻ እንደ ወጡ ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች። ባርነት፦ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ።
ከፍ ብዬ በጠቀስዃቸው ታሪኮች ቅደም ተከተል ከሄድን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ከሰይጣን ባርነት ነጻ ከማውጣቱ በፊት የሚቀድመው የሕዝበ እስራኤል ከግብጽ ባርነት ነጻ መውጣት ነው። ከነፍስ ነጻ መውጣት የሥጋ ነጻ መውጣት ቀድሟል ማለት ነው። ነገር ግን የእስራኤልንም ነጻነት ቢሆን ጠልቀን ብንመለከተው ከምድራዊ ገዢዎቻቸው ነጻ ከመውጣታቸው አስቀድሞ የነፍስ ነጻነት ማለትም የኅሊና ነጻነት ማግኘታቸውን እንረዳለን፤ ነጻነታቸውን በተግባር ከማግኘታቸው አስቀድሞ ራሳቸው ለራሳቸው ነጻነትን ሰጥተዋል። ይህንን ነው የኅሊና ነጻነት ያልኩት።
ማንኛውም ሰው ነጻነትን ከማግኘቱ አስቀድሞ ነጻነት እንደሚያስፈልገው ማወቅ፣ ማመን እና ከማንም ሰጪ ወገን እንዲቸረው ሳይጠብቅ ነጻነትን ለራሱ በራሱ መስጠት/ ማጎናጸፍ እንዳለበት ይሰማኛል። ለራሱ ነጻነት ያልሰጠ ሰው ሰዎች ቢሰጡትም ለመቀበል አይችልም። ማንነቱ ነጻነትን ለማስተናገድ ይሳነዋል። ነገር ግን ነጻነትን ለራሱ የሰጠ ሰው ሰዎች “ነጻነትህን ወስደንብሃል” ቢሉት እንኳን ነጻነትን ለራሱ ሊከለክልና ባሪያ ሊሆን አይቻለውም። አንድ ምሳሌ ልጥቀስ።
ሰውየው ለረዥም ዘመን በእስር ቤት የኖረ ነው አሉ። የዕድሜውን ግማሽ በላይ ያህል በእስር ቤት በመኖሩ እያንዳንዱ ርምጃው በእስር ቤቱ ኃላፊዎች ፕሮግራም ሲቀረጽለት የኖረ። የሚበላበት፣ የሚጠጣበት፣ የሚተኛበት፣ ሰውነቱን የሚታጠብበት፣ ሥራ የሚሔድበትና የሚመለስበት ጊዜ የተሰፈረና የተቆጠረ። ለእርሱ የምግብም ሆነ የመኝታ ሰዓት የሚወስኑት ሌሎች ሰዎች/ እስር ቤቱ ጠባቂዎች ናቸው። ይህንን ኑሮ ለረዥም ዘመን የተለማመደ ሰው አንድ ቀን “ነጻ ነህ፤ ወደ ቤትህ ሒድ” ተባለና ከወኅኒው ተለቀቀ።
ነገር ግን ሰውየው እስረኝነትን እንጂ ነጻነትን፣ በሰው ሰዓት መኖርን እንጂ በራሱ ሰዓት መሔድን አልለመደምና ነጻነቱ ባርነት ሆነበት። እስር ቤቱን ናፈቀ። የዕለት ኑሮውን ለማሸነፍ የተቀጠረበት ቦታ ያሉ አለቆቹን ሽንት ቤት ለመሔድ ያስፈቅድ ጀመር። ጥያቄው ግር የሚላቸው አለቆቹ “ታዲያ ሽንት ቤት ብትሔድ ባትሔድ እኛ ምን ቸገረን? ከገለግኽ ሒድ፣ ካልፈለግህ ቅር” ይሉታል። እርሱ ግን ሳያስፈቅዱ፣ ሌሎች ቡራኬ ሳይቸሩት የሚደረግ ኑሮን አያውቀው ኖሮ ነጻነት ከመርግ ከበደው። ባርነትን የተሸከመ ጫንቃው ነጻነትን ለመኖር ከበደው። (በግብጽ የባርነት ኑሮ መኖርን እንጂ ከፈርኦኖች አገዛዝ ውጪ ያለች አገር አልታይህ አለው።) ለካስ ሥጋው ነጻ ይሁን እንጂ ኅሊናውና ነፍሱ ገና እስረኞች ናቸው። የነፍስ ነጻነት ሳይኖር የሥጋ ነጻነት አይኖርም ያልኩትን ለማስረገጥ ፈልጌ ነው።
የቀደመውን ፋሲካ ያከበሩት ሕዝበ እስራኤል በሙሴ መሪነት ከግብጽ ባርነት እንዲወጡ ብዙ ተአምራት
ቢደረግላቸውም አዲሱን ነጻነት ለመቀበል ግን ሁሉም ዝግጁዎች አልነበሩም - ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን። የነጻነታቸውን ፈር ቀዳጅ
ሙሴን አንዴም ሲቀበሉት ሌላም ጊዜ ሲያሙት፣ አንዴ ሲያጸድቁት ሌላ ጊዜም ሲያዋርዱት ሲወጡ ሲወርዱ እንመለከታለን። በነጻነት ከሚያገኙት
መና ይልቅ በባርነት የሚሰጣቸውን የግብጽ ምግብ (ቅዱስ መጽሐፍ “ዓሣ፥ ዱባ፥ በጢኽ፥ ኩራት፥ ቀይ ሽንኩርት፥ ነጭ ሽንኩርት” ይለዋል) ይናፍቁ ነበር (ኦሪት ዘኍልቍ 11፥5)። ችግሩ
ግን ነጻነትን ያለማወቅ ዕዳ ነው።
12 comments:
ቃለ ሕይወት ያሰማለን እንዴት ነው ባክህ በዚህ ሰሞን እንደዚህ የዕውቀት ብርሃን ፍንትው ብሎ እየተቀጣጠለ ያለው። ጸጋውን ያብዛልህ።
"ነጻነትን የማናውቅ ነጻ ሕዝቦች ማለት እኛ ነን።" Dn. Epherem well said and interesting !!! Yibel yibel endil!!!!
Kale hiwotin yasemalin wondim Ephrem. Betam konjo new birtatun yistih.
እኛስ ብዙ ፋሲካ አያስፈልገንም? አንዱ ያንሰናል።
That is really true. I believe that there in no freedom of speech in Ethiopia. We need freedom of speech! Freedom ..............Thank you Dn Efrem Ewedihalehu. God Bless Ethiopia and Ethiopians!
Great insight! ነፃነት የሌለን ነፃ ባሮች ማለት እኛ ነን if there is such thing at all
Tsihufu tiru new. Neger gin Ethiopia wust minim netsanet endelele adrigeh silakerebkew, yeteganene meselegn. Mikiniyatum tinish ye Netsanet chilanchil yitayalina. Lemisale Yegil gazeta ende "Fitih" ayinet yemeselachewun yawim tekilay ministiruna amakariwochachew bedemb eyetechu yitsifalu. Endihum kezih befit be Atse Hailesilasse ena Be derg Yalineber ke 70 belay yetekawami party endefelegu mengistu yitechalu. Ena Ende America ayinet Netsanet endinoren bizu yemikeren bihonim, tinish yalechiwun netsanet eyadenikin mengist yebelete endiyashashil binigefafa tiru yimeslegnal. Betely ende ante yebetekiristiyan lij yehone ende chifin tekewamiwoch yalewun tinish lewti minim ende lele adrigo makireb, tirfu tizibt lay new yemitilih ena Le ewunet bitikom tiru yimeslegnal. Antem tinish netsanet silale yimeslegnal yihinin tsihufuh be Adis Guday metsihet yawetahew yimeslegnal.
sela netsanate asebalaho gene edemaya yaterale beya efaralaho
tabarake
ቃለ ህይወት ያሰማልን ረጅም እድሜ ይስጥልኝ
ይሄን ጽሁፍ በሸገር ራዲዮ ሲነበብ ስሰማው እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነበር ከዚያም ጽሁፍን ለማግኘት ተመኘሁ ወደአደባባይም ወጣሁ ተሳካልኝም
ምስጋና ለኤፍሬም
kale hiwoet yasemalin enameseginalen
kalehiwet yasemalin amen
Post a Comment